የድርጅቱ ታሪካዊ አመሰራረት
መግቢያሃገራችን ኢትዮጵያ የልማት ድርጅት ማቋቋም ከጀመረች በርካታ ዓመታት አስቆጥራለች፡፡ መንግስት በቀጥታ በማይገባባቸው ዘርፎች፣የዋጋ ንረትን ለማረጋጋት እና የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ፣ በርካታ ስራዎች ሲሰራ ቆይቷል፡፡ ስለሆነም ከአዲስ አበባ ንግድ ስራዎች ድርጅት ጋር ተመሳሳይ ይዘትና ባህሪት ያላቸው በርካታ ልማታዊ ድርጅቶች ተመስረተዋል እነርሱም ኢትዮጵያ ንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን ፣ የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ልማት ግብዓት አቅራቢ ድርድት፤ ኢትፋሩት እና በክልሎች መሰል ተቋማት በማቋቋም ወደ ስራ ከገቡ በርካታ ዘመንናት ተቆጥሯል ፡፡ ስለዚህ ከእነርሱ ልምድ በመውሰድ ከተማ አስተዳደሩ የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት በጥብቅ ዲሲፕሊን መምራትና ውጤት ማስመዝገብ አስፈላጊ ነው፡፡፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የልማት ድርጅቶች የሚመሩበት ሁኔታ ለመወሰንና ለማቋቋም ባወጣው ደንብ ቁጥር 14/1991 በከተማ አስተዳደሩ ባለቤትነት የማምረት፣ የማከፋፈል፣ አገልግሎት ለመስጠት የአስፈፃሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር እንደገና ለመወሰን ባወጣው አዋጅ ቁጥር 84/2016 መሰረት 10 የልማት ድርጅቶች ያቋቋመ ሲሆን ከዚህ ውስጥ አንዱ የአዲስ አበባ የንግድ ስራዎች ድርጀት በደንብ ቁጥር 152/2015 ዓ/ም በመመስረት የዋጋ ንረትን ለማረጋጋት ፣መንግስት የማያቀርባቸውን ምርትና አገልግሎቶች በጥናት በማረጋገጥ የመፍትሄ ሃሳብ በማቅረብ የተለያዩ የምርት ውጤቶችን ከተማ አስተዳደሩ በሚወጣው ታሪፍ መሰረት ለህብረተሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ(በትንሽ ትርፋ) በማቅረብ የተገልጋዩን እርካታ ማሳደግ የድርጅቱ ዋነኛው ተግባር ነው፡፡ታሪካዊ አመሰራረትየአዲስ አበባ የንግድ ሥራዎች ድርጅት በመነሻ ካፒታል ብር 7.25 ቢሊየን ሐምሌ 15/2015 ዓ/ም በደንብ ቁጥር 152 ተመሰረት፡፡ ድርጅቱ ለከተማ አስተዳደር ሸማቹ ህብረተሰብ የግብርና፣ የኢንዱስትሪ ምርቶችን እና የንግድ እቃዎችን በቀጥታ ከአምራቹ ጋራ የገበያ ትስስር በመፍጠር በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ አገልግሎት እንዲሰጥ የተቋቋመ ድርጅት ነ፡፡ በመጀመሪያ 1 አመት ጊዜ ውስጥ ወደ ብር 85,226,825.22 ብር በላይ ያልተጣራ ትርፍ ያገኘ ሲሆን ድርጅቱ ከከተማ አስተዳደሩ በተሰጠው ድጋፍ ቢሮና መጋዘን ያለው ሲሆን ለድጋፍና ክትትልም ምቹ ስፍራ ላይ ይገኛል፡፡ ድርጅቱ በደንብ ቁጥር 152/2015 ዓ.ም ቢቋቋምም ወደ ስራ የገባው ሚያዝያ 2016 ዓ.ም ነው፡፡ ድርጀቱ የመጀመሪያ ስራ አሰኪያጅ በሆኑት በአቶ መስፍን አሰፋ እየተመራ የገኛል፡፡በድረጅቱ የሚተዳደሩ ፋበሪካዎች |